ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል

 “ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል” ቢሚል ርዕስ ከባለ ድርሻ አካላት (ኦዲት ተደራጊ ተቋማት) አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ።

መጋቢት 23/2017 ዓ.ም

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መ/ቤት ከባለድርሻ አካላት (ኦዲት ተደራጊ ተቋማት) አመራሮች ጋር “ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማረጋገጥ የመንግስት ሀብትና ንብረትን ከብክነት እና ምዝበራ መከላከል”  በሚል ርዕስ ላይ በጁፒተር ሆቴል ውይይት አደረገ። ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ የውይይቱን ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን፤ በቀረበውም ሰነድ ላይ ተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም በቀረበው ጥያቄ ላይ  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ የተከበሩ አቶ ማሾ ኦላና እና ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ መቻሉ  ምላሽ ሰጥተውበት ውይይቱ ተጠናቅቋል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top