የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን አካሂዷል

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ያካሄደ ሲሆን፤ በጉባኤው የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተዋል ።
የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት ስለተሰሩ ሥራዎች፣ የመንገድ ማስፋፊያዎች የኮሪደር ልማቱን ተሞክሮ በመውሰድ በፍጥነት እና በጥራት እንዲጠናቀቁ እየተደረገ ሳላለው ክትትል፣ የመብራት መቆራረጥን በዘላቂነት ለመፍታት ምን ታስቧል? ፣ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት በተለይ የጤና ተቋማት ግንባታ ላይ የተለየ ትኩረት ቢሰጥ የሚሉ ጥያቄዎች ከተነሱት መካከል ይጠቀሳሉ።
እንደ ሀገር እየተዋወቀ ያለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ በአዲስ አበባ በፍጥነት እና በትኩረት ተግባራዊ ቢደረግ የሚሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎችም ከምክር ቤቱ አባላት ተነስተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከምክር ቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኢቢሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል


                   የኮሙንኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
                  ሚያዚያ 22/2017

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top